በቀቤና ልዩ ወረዳ መደበኛ ክትባት ሳይከተቡ ላመለጣቸው ህፃናት የክትባት ዘመቻ በሩሙጋ ቀበሌ ተጀምሯል ።
23 Oct 2025
በቀቤና ልዩ ወረዳ መደበኛ ክትባት ሳይከተቡ ላመለጣቸው ህፃናት የክትባት ዘመቻ በሩሙጋ ቀበሌ ተጀምሯል ።
23 Oct 2025
በቀቤና ልዩ ወረዳ መደበኛ ክትባት ሳይከተቡ ላመለጣቸው ህፃናት የክትባት ዘመቻ በሩሙጋ ቀበሌ ተጀምሯል ።
ወልቂጤ ፣ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት በልዩ ወረዳው በሩሙጋ ቀበሌ የተቀናጀ የጤና ስራ እና ክትባት ያልተከተቡና ጀምረው ያቋረጡ ህፃናትን ክትባት መስጠት ጀምሯል ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የህክምና አገልግሎት ዳሬክቶሬት ዳሬክተር የሆኑት ዶ/ር ዳዊት ዳንኤል እንደገለፁት ከጥቅምት 13- 22/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 10 ቀናት በሚደረገው የተፋጠነ እና ታላሚ ተኮር የማካካሻ ክትባት ዘመቻ በዋናነት በክልሉ 102,122 ክትባት አገልግሎት ላላገኙ ፣ 945,00 ክትባት ጀምረው ላቋረጡ እንዲሁም 193,309 ተከታታይ የኩፍኝ ክትባት ያመለጣቸውን ህፃናት ለማድረስ የተዘጋጀ እንደሆነ ጠቁመዋል።
እንደ ቀቤና ልዩ ወረዳ 771 ያልተከተቡ ፣ 102 ጀምረው ያቋረጡ እንዲሁም ከ2,000 በላይ ተከታታይ የኩፍኝ ክትባት ያልወሰዱ ህፃናትን በዘመቻው ለመከተብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን በመግለፅ ክትባቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል ።
ኃላፊው አክለውም ከክትባቱ ጎን ለጎን የወባ መከላከልና መቆጣጠር፣ የማህፀን ውልቃትና መሸንቆር ልየታ፣ የማህፀን በር ካንሰር ልየታና ህክምና እንዲሁም የከፋ የምግብ እጥረት ልየታና ህክምና ለህፃናት፣ ለነፍሰጡር እና አጥቢ እናቶች እንደሚደረግ ተናግረዋል ።
የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብድልሀይ ኑርሀሰን እንደተናገሩትም የዛሬው ዘመቻ እንደ ሀገርና ክልላችን የተቀናጀ የክትባት አገልግሎት ዘመቻ የተከፈተበት ቀን መሆኑን በመጠቆም በልዩ ወረዳው በ24ቱም ቀበሌዎች ለተከታታይ 10ቀናት የሚሰጥ መሆኑን ገልፀዋል ።
********
በፀጋዬ አረጋ
**
#ውጤታማ የመረጃ ልውውጥ ለልማት !
ፈጣንና ትኩስ መረጃዎችን በሌሎች የሚዲያ አማራጮች ይጠቀሙ‼️
👉Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=100072292788562&mibextid=ZbWKwL
👉Instagram https://www.instagram.com/qebenacomm?igsh=NHRiZjFybHk4dmRn
👉Twitter https://x.com/KebenaO88374?t=T_ncptfwuNAwRnhxrqdM9w&s=09
👉Telegram channel
https://t.me/Qebena1
👉youtube
https://youtube.com/@kebenaspecialworedacomm?si=DOrrIJYDBKMzjXCr
👉tiktok
tiktok.com/@kebenacommunication
👉email :- kebenaworedacommunicationaffai@gmail.com
ወልቂጤ ፣ጥቅምት 13/2018 ዓ.ም
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት በልዩ ወረዳው በሩሙጋ ቀበሌ የተቀናጀ የጤና ስራ እና ክትባት ያልተከተቡና ጀምረው ያቋረጡ ህፃናትን ክትባት መስጠት ጀምሯል ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የህክምና አገልግሎት ዳሬክቶሬት ዳሬክተር የሆኑት ዶ/ር ዳዊት ዳንኤል እንደገለፁት ከጥቅምት 13- 22/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 10 ቀናት በሚደረገው የተፋጠነ እና ታላሚ ተኮር የማካካሻ ክትባት ዘመቻ በዋናነት በክልሉ 102,122 ክትባት አገልግሎት ላላገኙ ፣ 945,00 ክትባት ጀምረው ላቋረጡ እንዲሁም 193,309 ተከታታይ የኩፍኝ ክትባት ያመለጣቸውን ህፃናት ለማድረስ የተዘጋጀ እንደሆነ ጠቁመዋል።
እንደ ቀቤና ልዩ ወረዳ 771 ያልተከተቡ ፣ 102 ጀምረው ያቋረጡ እንዲሁም ከ2,000 በላይ ተከታታይ የኩፍኝ ክትባት ያልወሰዱ ህፃናትን በዘመቻው ለመከተብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን በመግለፅ ክትባቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል ።
ኃላፊው አክለውም ከክትባቱ ጎን ለጎን የወባ መከላከልና መቆጣጠር፣ የማህፀን ውልቃትና መሸንቆር ልየታ፣ የማህፀን በር ካንሰር ልየታና ህክምና እንዲሁም የከፋ የምግብ እጥረት ልየታና ህክምና ለህፃናት፣ ለነፍሰጡር እና አጥቢ እናቶች እንደሚደረግ ተናግረዋል ።
የቀቤና ልዩ ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብድልሀይ ኑርሀሰን እንደተናገሩትም የዛሬው ዘመቻ እንደ ሀገርና ክልላችን የተቀናጀ የክትባት አገልግሎት ዘመቻ የተከፈተበት ቀን መሆኑን በመጠቆም በልዩ ወረዳው በ24ቱም ቀበሌዎች ለተከታታይ 10ቀናት የሚሰጥ መሆኑን ገልፀዋል ።
********
በፀጋዬ አረጋ
**
#ውጤታማ የመረጃ ልውውጥ ለልማት !
ፈጣንና ትኩስ መረጃዎችን በሌሎች የሚዲያ አማራጮች ይጠቀሙ‼️
👉Facebook https://www.facebook.com/profile.php?id=100072292788562&mibextid=ZbWKwL
👉Instagram https://www.instagram.com/qebenacomm?igsh=NHRiZjFybHk4dmRn
👉Twitter https://x.com/KebenaO88374?t=T_ncptfwuNAwRnhxrqdM9w&s=09
👉Telegram channel
https://t.me/Qebena1
👉youtube
https://youtube.com/@kebenaspecialworedacomm?si=DOrrIJYDBKMzjXCr
👉tiktok
tiktok.com/@kebenacommunication
👉email :- kebenaworedacommunicationaffai@gmail.com
ተጨማሪ ምስሎች